ግስ የሚለውን ቃል ለመረዳት፦ ፩ ገሰ ወይም ገሰሰ – ዳሰሰ፤ ዳበሰ፤ በእጁ ነካ፤ አረጋገጠ ማለት ነው። ገሲስ ገሲሶት ንዜንወክሙ በእንተ ውእቱ ዘሀሎ እምቅድም ዘሰማዕናሁ በእዘኒነ ወዘርኢናሁ በአዕይንቲነ ወዘጠየቅናሁ “ወዘገሰሳሁ እደዊነ” – ከመጀመሪያ ስለነበረው፣ በጆሯችን ስለሰማነው፣ በዐይናችን ስላየነው፣ ስለተረዳነው፣ “በእጆቻችን ስለዳሰስነው” እንነግራችኋለን ፩ዮሐ ፩፥፩
ማስረጃ ጥቅሶች፦
ኢትግስሱ መሢሐንየ – የቀባኋቸውን አትዳሱ/አትንኩ መዝ ፻፬፥፲፭
“ርእዩ እደውየ ወእገርየ ከመ አነ ውእቱ ወግሥሡኒ ወአእምሩ – እጄንና እግሬን እዩ ዳሱኝም እኔ እንደሆንሁም እወቁ” ሉቃ ፳፬፥፴፱
ከላይ ያየነውን መነሻ አድርገን ግስ ማለት፦
፦ ግስ መግሰስ፣ አንዱን ቃል ማርባት፣ ማብዛት፣ የሩቁን ለቅርብ፣ የወንዱን ለሴት፣ ያንዱን ለብዙ መስጠት ማወራረስ ማለት ነው።
፦ የቋንቋ ጓዝ የዘርና የነባር እክት ወይም ስብስብ/ምእላድ ማለት ነው።
“ሰማይ ከነግሱ ምድር ከነልብሱ” እንዲሉ ከነጓዙ ለማለት።
፦ የቋንቋ መጽሐፍ፣ የዘርና የነባር መድበል፣ መዝገበ ቃል፣ ንባቡ በፊደል የታከተ የተከተተ ማለት ነው።
በሌላ አተረጓጐም፦
መፋቅ፣ መፈቅፈቅ፣ ማጥፋት የሚል ትርጒም አለው።
ፈኑ እዴከ ወግስስ – እጅህን ዘርጋ ዳሰውም (ያለውን ሁሉ አጥፋበት) ኢዮ ፩፥፲፩
በገሰ ወይም በገሰሰ የግስ አወራረድ
ገሰ፤ ገሰሰ፤ ይገስስ – ይግስስ – ይግስስ
ሣልስ ቅጽል፦ (የመጨረሻው ፊደል ሣልስ የሆነ ማለት ነው፤ ለምሳሌ፦ ሀ ግእዝ፣ ሁ ካዕብ፣ ሂ ሣልስ)
ገሳሲ፣ ገሳስያን፣ (ለወንድ)
ገሳሲት፣ ገሳስያት፣ (ለሴት)
ሳድስ ቅጽል ወይም ውስጠዘ (የመጨረሻው ፊደል ሳድስ የሆነ ማለት ነው፤ ለምሳሌ፦ ሀ ግእዝ፣ ሁ ካዕብ፣ ሂ ሣልስ፣ ሃ ራብዕ፣ ሄ ሐምስ፣ ህ ሳድስ)
ግሱስ፣ግሱሳን፣(ለወንድ)
ግስስት፣ ግሱሳት (ለሴት)
ባዕድ ቅጽል፦
መግስስ፣ መግስሳን፣ (ለወንድ)
መግስስት፣ መግስሳት (ለሴት)
መድበል ቅጽል፦
ገሰስት (ለወንድም ለሴትም)
ግሰት (ጥ) – መዳሰስ፣ አደሳሰስ፣ ዳሰሳ፣ ዳበሳ
ግሳሴ (ጥሬ ዘር)



Leave a Reply