፩ መዝሙር ዮሐንስ አኅድዐ

Published by

on

፩.፩ መዝሙር ዮሐንስ አኅድዐ ከመስከረም ፩ – መስከረም ፯

(በ፭/ን) ዮሐንስ አኅድዐ እምካልአኒሁ አንሐ ወክሐ እንዘ ይብል እምላዕሉ ወረደ ቃለ አብ ወተሐውከ ማየ ዮርዳኖስ እምግርማ መለኮት ወደንገጹ ኵሉ ኃይለ ሰማያት ወምድር ከማሁ ኮነ በቢታንያ በቤተ ራማ በማዕዶተ ዮርዳኖስ ወሶበ ርእዮ ዮሐንስ ለኢየሱስ ከልሐ ወይቤ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ይቤሎ ኢየሱስ ለዮሐንስ አጥምቀኒ በማይ ከመ ይትቀደስ ማይ በማዕተበ ሰማይ አጥመቆ ዮሐንስ ለኢየሱስ በፈለገ ዮርዳኖስ እምድኅረ አጥመቀ ለሊሁ ተጠምቀ ምህሮሙ ለሕዝብ ወይቤሎሙ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ።

ትርጕም፦

ዮሐንስ ከወንድሞቹ ይልቅ ጸጥ አሰኘ ከሌሎቹ ተለይቶ አብዝቶና አሰምቶ ተናገረ እንዲህ ብሎ አስተማረ የአብ አካላዊ ቃል ከሰማያት ወረደ፤ ከመለኮታዊ ግርማው የተነሣ የዮርዳኖስ ውኃ ታወከ ብሎ። በቢታንያ፣ በቤተ ራባና በዮርዳኖስ ማዶ ሁሉ እንዲሁ አሰምቶ ተናገረ። ዮሐንስ ጌታ ኢየሱስን ባየው ጊዜ የእግዚአብሔር በግ እነሆ ብሎ ጮኾ ተናገረ። ጌታ ኢየሱስም ዮሐንስን በሰማያዊ በረከት/በመለኮታዊ ሥልጣን ይባረክ/ይከብር ዘንድ በውኃ አጥምቀኝ አለው። ዮሐንስ ጌታችንን በዮርዳኖስ ወንዝ አጠመቀው። ከአጠመቀ በኋላ ራሱ ተጠመቀ። ሕዝቡን ሰንበትን አክብሩ የጽቅድንም ሥራን ሥሩ ብሎ አስተማራቸው። 

፩.፪ የዕለቱ ምንባባት፦ 

፩ቆሮ ፲፩፥፲፯ -ፍጻሜ፤ 

ያዕ ፪፥፩ – ፲፬፤ 

ግብ ፲፰፥፳፬ – ፍጻሜ፤ 

ወንጌል፦ ዮሐ ፩፥፲፭ – ፴፰፤

ቅዳሴ፦ ዘአትናቴዎስ 

፩.፫ የዕለቱ ምስባክ፦

ሣህል ወርትዕ ተራከባ፤

ጽድቅ ወሰላም ተሰዓማ፤

ርዕትሰ እምድር ሠረፀት። መዝ ፹፬፥፲፤

ትርጉም፦

ይቅርታና እውነት ተገናኙ፤

ጽድቅና ሰላም ተስማሙ፤

ቅንነት ከምድር በቀለች።

ምሥጢር፦

ሊቀ ካህናቱ በግብረ ክህነት ንጉሡ በግብረ መንግሥት ተገናኙ፤ ንጉሡ ይፈርዳል ይተቻል፤ ሊቀ ካህናቱ መንፈሳዊ ትምህርት ያስተምራል።

አንድም ጌታችን ለመጠመቅ ዮሐንስ ለማጥመቅ በዮርዳኖስ ተገናኙ፤ ዮሐንስ ምድራዊ ልደቱንና ምድራዊ ቤተ ሰቡን ይናገራል፤ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ ይበረታል እኔ በውኃ አጠምቃችኋለሁ እያለ ያስተምራል፤ ጌታ ግን ከሰማይ መጣሁ ከሰማይ የወረደ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ እያለ ያስተምራል። 

አንድም መለኮትና ትስብእት በማኅፀነ ማርያም ተገናኙ ማለት ምሥጢረ ተዋሕዶ ተከናወነ፤ ኤልሳቤጥና እመቤታችን በቤተ ዘካርያስ ተገናኙ፤ “ወቦአት ቤተ ዘካርያስ ወአምኃታ ለኤልሳቤጥ – ወደዘካርያስ ቤት ገብታ እልሳቤጥን እጅ ነሣቻት” እንዲል። ሉቃ ፩፥፵፤ 

Leave a Reply

Discover more from በመካነ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ኤላም የትምህርት ማዕከል

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading